Contact me

  • Contact me via hawiti@yahoo.com or hawiolani@gmail.com

Sunday, November 3, 2013

አሳዛኝ ዜና- ስደተኞቹ በሙሉ አለቁ!

ከኒጀር ተነስተው ፣ ሰሃራ በረሃን በማቋረጥ አልጄሪያ ለመድረስ፣ ከዚያም ወደ ሌላ አገር ለመሻገር አንድ መቶ የሚሆኑ ስደተኞች በአንድ መኪና ታጭቀው ጉዞ ይጀምራሉ።
ሰሃራ በረሃን እንዳጋመሱ የተጫኑበት መኪና ይበላሻል። በዚያ በረሃ፣ መኪና ጠጋኝ ቀርቶ ፣ ቀና ቢሉ ሰማይ፣ ጎንበስ ቢሉ ድንጋይ ካልሆነ ምንም አልነበረም። የሚያደርጉት ጠፋቸው። ማንም የሚደርስላቸውም አልነበረም። በዚህ ሁኔታ ቀናት ተቶጠሩ። የቋጠሯት ጭብጦና እፍኝ ውሃ አለቀች። ቀስ በቀስም አንድ በአንድ እያሉ በውሃ ጥምና በረሃብ ይሞቱ ጀመር።
በመጨረሻም አንድ ዘላን ድንገት ሲያልፍ ያየውን በመናገሩ በሂሊኮፕተር ከስፍራው ሲደረስ ሁሉም፣ አንድም ሳይቀር፣ በውሃ ጥም ሞተውና ወድቀው፣ አንዳንዶቹም ባልታወቀ አውሬ ተበልተው ተገኙ። የበለጠ የሚያሳዝነው 92ቱ ሴቶችና ህጻናት ናቸው። ዜናውን ሲ ኤን ኤን ዛሬ ኦክቶበር 31 አወራው -

No comments:

Post a Comment